ከኢየሱስ ተማሩ
ለአምላክ ጊዜ ስጥ
ለአምላክ ጊዜ ስትሰጥ ሕይወትህ ይሻሻላል። በውስጥህ ያለው መንፈሳዊ ጥማትም ይረካል። ኢየሱስ ስለዚህ ርዕሰ ጉዳይ ምን እንዳስተማረ ተመልከት።
ኢየሱስ ምን አስተምሯል?
“መንፈሳዊ ነገሮችን የተጠሙ ደስተኞች ናቸው።”—ማቴዎስ 5:3
‘ወደዚህ ምድር የመጣነው ለምንድን ነው? መከራችን የበዛው ለምንድን ነው? ሰው ሲሞት ምን ይሆናል?’ እነዚህ የሁላችንም ጥያቄዎች ናቸው። ደስተኛ መሆናችን የተመካው ለእነዚህ ጥያቄዎች በምናገኘው አርኪ መልስ ላይ ነው።
“ሰው ከይሖዋa አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በምግብ ብቻ አይኖርም።”—ማቴዎስ 4:4
የሰው ልጅ በሕይወት ለመኖር ምግብ እንደሚያስፈልገው ሁሉ መንፈሳዊ ምግብም ያስፈልገዋል። የኢየሱስ ሐሳብ እንደሚጠቁመው መንፈሳዊ ረሃባችንን ለማስታገሥ አዘውትረን የአምላክን እርዳታ መፈለግ አለብን።
“ቃልህ እውነት ነው።”—ዮሐንስ 17:17
መንፈሳዊ ፍላጎታችንን እንድናረካ አምላክ እኛን የሚያግዝበት ዋነኛው መንገድ ቃሉ ማለትም መጽሐፍ ቅዱስ እንደሆነ ኢየሱስ ጠቁሞናል።
አንተስ ዘላቂ ደስታ ማግኘት ትፈልጋለህ? ለአምላክ ጊዜ እንድትሰጥና መንፈሳዊ ጥማትህን እንድታረካ እናበረታታሃለን። ይህን ለማድረግ የሚያግዙ ነገሮችን አዘጋጅተንልሃል፤ ለምን አትሞክራቸውም?
በግል በሚመደብልህ አስተማሪ አማካኝነት አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮርሳችንን በነፃ ተማር።
a ይሖዋ የአምላክ ስም ነው። (መዝሙር 83:18) “ይሖዋ ማን ነው?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።