የጥያቄ ሣጥን
◼ አንድን ሰው መጽሐፍ ቅዱስን ማስጠናታችንን ማቋረጥ ተገቢ የሚሆነው መቼ ነው?
ተማሪው ምንም ዓይነት መንፈሳዊ እድገት የማያደርግ ከሆነ በዘዴ ጥናቱን ማቋረጥ ሊኖርባችሁ ይችላል። (ማቴ. 10:11) እስቲ የሚከተሉትን ነጥቦች አስቡ፦ የጥናት ፕሮግራሙን አክብሮ ይገኛል? ትምህርቱን አስቀድሞ ይዘጋጃል? አልፎ አልፎ በጉባኤ ስብሰባዎች ላይ ይገኛል? የተማረውን ነገር ለሌሎች ለመናገር ጥረት ያደርጋል? ከመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች ጋር ለመስማማት ሲል አንዳንድ ለውጦች እያደረገ ነው? እርግጥ ነው፣ ሁሉም ሰው እድገት የሚያደርግበት ፍጥነት አንድ እንዳልሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል፤ በመሆኑም ዕድሜውንና ችሎታውን ግምት ውስጥ ማስገባት ተገቢ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ጥናቱን ለማቋረጥ ከወሰናችሁ፣ ተማሪው ዝግጁ በሚሆንበት ጊዜ ጥናቱን ለመቀጠል ፈቃደኛ እንደሆናችሁ አሳውቁት።—1 ጢሞ. 2:4