ለጥናት የሚረዱ ሐሳቦች
የመጽሐፍ ቅዱስን ዘይቤያዊ አገላለጾች መረዳት
መጽሐፍ ቅዱስ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዘይቤያዊ አገላለጾችን ይዟል። ብዙ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን ሲያነቡ እነዚህን ዘይቤያዊ አገላለጾች ለመረዳት ይቸገራሉ። (ማቴ. 13:13) ታዲያ ትርጉማቸውን ለመረዳት ምን ያግዘናል?
ርዕሰ ጉዳዩን እና ምሳሌውን ለይ። ዘይቤያዊ አገላለጾች አንድን ርዕሰ ጉዳይ ከአንድ ምሳሌ ጋር ያወዳድራሉ። ለምሳሌ ያህል፣ ራእይ 3:3 የኢየሱስን መምጣት (ርዕሰ ጉዳይ) ከሌባ አመጣጥ (ምሳሌ) ጋር ያመሳስለዋል።
ርዕሰ ጉዳዩ ከምሳሌው ጋር የሚመሳሰለው እንዴት እንደሆነ አስተውል። ሁለቱ ነገሮች ለምን እንደተወዳደሩና የሚመሳሰሉት በየትኞቹ አቅጣጫዎች እንደሆነ ለማሰብ ሞክር።
ትክክለኛው መደምደሚያ ላይ መድረስህን አረጋግጥ። አንዳንዴ ርዕሰ ጉዳዩን ከምሳሌው ጋር ባልተፈለገ መንገድ ካመሳሰልነው የተሳሳተ መደምደሚያ ላይ ልንደርስ እንችላለን። ለአብነት ያህል፣ ከላይ በተጠቀሰው ምሳሌ ላይ የኢየሱስ መምጣት ከሌባ ጋር የተወዳደረው አመጣጡ ያልተጠበቀና ድንገተኛ እንደሚሆን ለማጉላት እንጂ ኢየሱስ የሆነ ነገር እንደሚሰርቅ ለመጠቆም አይደለም።