የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w26 የካቲት ገጽ 32
  • አብድዩ—አምላካዊ ፍርሃት አዳብር

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • አብድዩ—አምላካዊ ፍርሃት አዳብር
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2026
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • እምነትና አምላካዊ ፍርሃት የሚያስገኘው ድፍረት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2006
  • ይሖዋን መፍራት የሚኖርብን ለምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2023
  • የአብድዩ፣ የዮናስ እና የሚክያስ መጻሕፍት ጎላ ያሉ ነጥቦች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2007
  • ይሖዋን በመፍራት ደስታ ማግኘትን መማር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1995
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2026
w26 የካቲት ገጽ 32

የመጽሐፍ ቅዱስ ባለታሪክ

አብድዩ—አምላካዊ ፍርሃት አዳብር

አብድዩ በንጉሥ አክዓብ ቤት ላይ አዛዥ ነበር። ክፉው ንጉሥ አክዓብ አስጸያፊ የሆነው የባአል አምልኮ በምድሪቱ እንዲስፋፋ ፈቅዶ ነበር። አብድዩ ግን ‘ከወጣትነቱ ጀምሮ’ ይሖዋን ይፈራ ነበር። (1 ነገ. 18:1-13) በመሆኑም ንግሥት ኤልዛቤል ሁሉም የይሖዋ ነቢያት እንዲገደሉ ትእዛዝ ስታስተላልፍ አብድዩ እነሱን ለመርዳት በድፍረት እርምጃ መውሰድ እንዳለበት ተገነዘበ። በወቅቱ አንድ ነቢይ መደበቅ እንኳ አደገኛ ነበር፤ አብድዩ ግን 100 ነቢያትን የደበቀ ከመሆኑም ሌላ ከባድ ረሃብ በተከሰተበት ወቅት ይመግባቸው ነበር! ንጉሡንና ንግሥቲቱን የሚያገለግሉት በመቶዎች የሚቆጠሩ የሐሰት ነቢያት ሳያዩት ይህን ማድረግ ምን ያህል ከባድ ሊሆን እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም።—1 ነገ. 18:19

እኛስ ፈሪሃ አምላክ ከነበረው ከዚህ ሰው ምን ትምህርት እናገኛለን? አብድዩ አክዓብን ይፈራው የነበረ ቢሆንም ለአምላክ የነበረው ፍርሃት ግን ከዚህ የላቀ ነበር። ይህም ሕይወቱን አደጋ ላይ ጥሎ ወንድሞቹን እንዲታደግ ድፍረት ሰጥቶታል። እኛም በምንኖርበት አካባቢ በእውነተኛው አምልኮ ላይ እገዳ ከተጣለ አምላካዊ ፍርሃት ማዳበር እንችላለን። እንዲህ ያለው ፍርሃት በፈተና ውስጥ ያሉ ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን ለመደገፍ ብርታት ይሰጠናል።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2026)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2026 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ