የካቲት 3 የሚጀምር ሳምንት ፕሮግራም
የካቲት 3 የሚጀምር ሳምንት
መዝሙር 22 እና ጸሎት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
cf ምዕ. 18 ከአን. 10-18 (30 ደቂቃ)
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ ዘፍጥረት 21–24 (10 ደቂቃ)
ቁ. 1፦ ዘፍጥረት 23:1-20 (4 ደቂቃ ወይም ከዚያ በታች)
ቁ. 2፦ ኢየሱስ ሥጋዊ አካል ለብሶ የታየው ለምንድን ነው?—rs ገጽ 334 አን. 1-4 (5 ደቂቃ)
ቁ. 3፦ አቤል—አምላክን የሚያስደስት እምነት ማሳየት—w13 1/1 ገጽ 12-15 (5 ደቂቃ)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
10 ደቂቃ፦ በየካቲት ወር መጽሔቶችን አበርክቱ። በውይይት የሚቀርብ። በቅድሚያ በገጽ 4 ላይ የሚገኙትን የአቀራረብ ናሙናዎች በመጠቀም እያንዳንዱን መጽሔት እንዴት ማበርከት እንደሚቻል የሚያሳዩ ሠርቶ ማሳያዎች እንዲቀርቡ አድርግ። ከዚያም በአቀራረብ ናሙናዎቹ ውስጥ የሰፈረውን እያንዳንዱን ሐሳብ ተራ በተራ ተወያዩበት፤ ይህን ለማድረግ በአንድ ጊዜ አንድ ወይም ሁለት ዓረፍተ ነገር ብቻ በማንበብ አድማጮች ሐሳቡ የተጠቀሰበትን ምክንያት እንዲያብራሩ መጋበዝ ይቻላል። አስፋፊዎቹ አቀራረቡን ቃል በቃል ከመሸምደድ ይልቅ የራሳቸውን አባባል እንዲጠቀሙ አሳስባቸው፤ እንዲሁም የአቀራረብ ናሙናውን ትንሽ ለወጥ አድርገው መጠቀም ወይም ሌላ አቀራረብ ማዘጋጀት ሊመርጡ ይችላሉ። ሁሉም ከመጽሔቶቻችን ጋር በደንብ እንዲተዋወቁና በቅንዓት እንዲያሰራጩ አጠር ያለ ማበረታቻ በመስጠት ክፍልህን ደምድም።
10 ደቂቃ፦ ለጉባኤው እንደሚያስፈልግ ተጠቀሙበት። “ራሳቸውን በፈቃደኝነት አቅርበዋል” በሚለው w13 10/15 ገጽ 3-6 ላይ በሚገኘው ርዕስ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። ለጉባኤያችሁ ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉ ነጥቦችን አጉላ።
10 ደቂቃ፦ በፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ። (ማቴ. 7:16) በ2013 የዓመት መጽሐፍ (እንግሊዝኛ) ገጽ 47 አንቀጽ 1-2 እንዲሁም ከገጽ 52 አንቀጽ 1 እስከ ገጽ 53 አንቀጽ 1 ላይ ተመሥርቶ በውይይት የሚቀርብ። አድማጮች ምን ትምህርት እንዳገኙ ጠይቅ።
መዝሙር 25 እና ጸሎት