ሐምሌ 19 የሚጀምር ሳምንት
ሐምሌ 19 የሚጀምር ሳምንት
□ የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፦
lv ምዕ. 16 አን. 9-14፤ በገጽ 192 እና 193 ላይ የሚገኘው ሣጥን
□ ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት፦
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፦ 1 ነገሥት 12-14
ቁ. 1፦ 1 ነገሥት 12:12-20
ቁ. 2፦ ወንድሞቻችንን በይሖዋ ዓይን እንድናያቸው ምን ሊረዳን ይችላል?
ቁ. 3፦ ከይሖዋ ጋር የመሠረታችሁትን ወዳጅነት እንደ ውድ ሀብት በመመልከት ከመጥፎ ጓደኞች ራቁ (rs ገጽ 189 አን. 3)
□ የአገልግሎት ስብሰባ፦
5 ደቂቃ፦ ማስታወቂያዎች።
10 ደቂቃ፦ አገልግሎትህን ማስፋት የምትችልባቸው መንገዶች—ክፍል 2። የተደራጀ ሕዝብ በተባለው መጽሐፍ ገጽ 112 አንቀጽ 3 እስከ ገጽ 113 አንቀጽ 2 ባለው ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ የሚቀርብ ንግግር። አቅኚ ለመሆን ሲሉ ፕሮግራማቸውን ማስተካከል የቻሉት እንዴት እንደሆነ እንዲናገሩ ለአንድ ወይም ለሁለት አቅኚዎች ቃለ ምልልስ አድርግ።
10 ደቂቃ፦ ለሚቀጥለው የትምህርት ዘመን መዘጋጀት የምትችሉት እንዴት ነው? ከአድማጮች ጋር በሚደረግ ውይይት የሚቀርብ። ክርስቲያን ወጣቶች በትምህርት ቤት የሚያጋጥሟቸውን አንዳንድ ተፈታታኝ ሁኔታዎች እንዲናገሩ አድማጮችን ጋብዝ። ወላጆች ልጆቻቸው በትምህርት ቤት የሚያጋጥሟቸውን ፈተናዎች መቋቋምና ስለ እምነታቸው ማስረዳት እንዲችሉ ከወዲሁ ለማዘጋጀት በቤተሰብ አምልኮ ወቅት የመጠበቂያ ግንብ ማኅበር ጽሑፎች ማውጫን፣ የወጣቶች ጥያቄ የተባሉትን መጻሕፍትና ሌሎች ቲኦክራሲያዊ መሣሪያዎችን እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ተናገር። (1 ጴጥ. 3:15) ከዚህ ጋር በተያያዘ አንድ ወይም ሁለት ርዕሰ ጉዳዮች ምረጥና ከጽሑፎቻችን ያገኘሃቸውን አንዳንድ ጠቃሚ ሐሳቦች ተናገር። ትምህርት ቤት እያሉ እንዴት ምሥክርነት ይሰጡ እንደነበር እንዲናገሩ አድማጮችን ጋብዝ።
10 ደቂቃ፦ “የምችለውን ያህል እያደረግኩ ነው?” በጥያቄና መልስ የሚቀርብ።