መዝሙር 162
ልቤ ቃሉን ይጠማል
በወረቀት የሚታተመው
(ማቴዎስ 5:3)
1. ሰው ሲፈጠር ከጥንቱ፣
አኑሮለት መሻቱን።
ይዋትታል በፍለጋ፣
አምላኩን ሊጠጋ።
እሱ መች ተሰውሮ፤
ቅርብ ነበር ከድሮ።
ራሱን ገልጦ፣ ቃሉን ሰጥቶ፣
ተገኘልኝ ወዶ።
(አዝማች)
ለሱ፣ ’ኖራለሁ ለሱ፤
ፈቅ አልልም ከትዛዙ።
ስሙን አወድሳለሁ፣
በሕይወት እስካለሁ።
ልቤ ’ሱን ይሻል፤
ቃሉን ይጠማል።
2. ቀን አልፎ ቀን ሲተካ፤
ቃልህ አዲስ ነው ለካ!
አልለየውም ከሐሳቤ፤
ሆኗል የ’ለት ምግቤ።
ዝም አልልም ፈጽሞ፣
ቃልህ ተገኝቶ ደግሞ።
ልክ እንደኔ ይደሰቱ፤
ቅኖች ነፃ ይውጡ።
(አዝማች)
ለሱ፣ ’ኖራለሁ ለሱ፤
ፈቅ አልልም ከትዛዙ።
ስሙን አወድሳለሁ፣
በሕይወት እስካለሁ።
ልቤ ’ሱን ይሻል፤
ቃሉን ይጠማል።
ለሱ፣ ’ኖራለሁ ለሱ፤
ፈቅ አልልም ከትዛዙ።
ስሙን አወድሳለሁ፣
በሕይወት እስካለሁ።
ልቤ ’ሱን ይሻል፤
ቃሉን ይጠማል።
ለሱ፣ ’ኖራለሁ ለሱ፤
ፈቅ አልልም ከትዛዙ።
ስሙን አወድሳለሁ፣
በሕይወት እስካለሁ።
ልቤ ’ሱን ይሻል፤
ቃሉን ይጠማል።
(በተጨማሪም መዝ. 1:1, 2፤ 112:1፤ 119:97፤ ኢሳ. 40:8፤ ማቴ. 5:6፤ 16:24፤ 2 ጢሞ. 4:4ን ተመልከት።)