የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w26 መጋቢት ገጽ 32
  • እንደ በናያህ ደፋርና ታማኝ ሁን

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • እንደ በናያህ ደፋርና ታማኝ ሁን
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2026
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ከይሖዋ ታማኝ አገልጋዮች ትምህርት ማግኘት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
  • “ፈቃድህን እንድፈጽም አስተምረኝ”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
  • እንደ ሳዶቅ ደፋር ሁን
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2024
  • ‘ታማኝ መሆንህን ታሳያለህ’
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2010
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2026
w26 መጋቢት ገጽ 32

የመጽሐፍ ቅዱስ ባለታሪክ

እንደ በናያህ ደፋርና ታማኝ ሁን

በናያህ ንጉሥ ዳዊትንና ንጉሥ ሰለሞንን ያገለግል የነበረ ደፋር ተዋጊ ነው። በናያህ የካህን ልጅ ነበር። በአብዛኛው ካህናትና ሌዋውያን በጦርነት አይካፈሉም፤ የጦር መሣሪያም አይዙም። በናያህ ግን በይሖዋ ስም በሚደረጉ ጦርነቶች ላይ ይካፈል ነበር። በናያህ አስደናቂ ድፍረት አሳይቷል። ለምሳሌ ወደ አንድ የውኃ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ወርዶ አንበሳ ገድሏል፤ እንዲሁም መሣሪያ የታጠቀን አንድ ግዙፍ ወታደር አሸንፏል። ዳዊት በናያህን በጣም ያምነው ስለነበር የራሱ የክብር ዘብ አለቃ አድርጎ ሾሞታል።—2 ሳሙ. 23:20-23

አቢሴሎምና አዶንያስ ባመፁበት ወቅት በናያህ ለዳዊት ታማኝ ሆኖ ቀጥሏል። (2 ሳሙ. 8:18፤ 15:18፤ 1 ነገ. 1:8) ዳዊት ባረጀ ጊዜም በናያህ ሰለሞን እንዲነግሥ በማድረግ ለዳዊት ያለውን ታማኝነት አሳይቷል። (1 ነገ. 1:32-40) ሌሎች ታማኝ ሳይሆኑ በቀሩበት ጊዜም ጭምር በናያህ ለይሖዋና እሱ ለሾማቸው ሰዎች ታማኝ ሆኖ ኖሯል።

እኛም ኃያል ከሆነው ጠላታችን ከሰይጣንና ከግብረ አበሮቹ ጋር ለመዋጋት ድፍረት ያስፈልገናል። በተጨማሪም በይሖዋ መሥፈርቶች ለመመራት ቁርጥ ውሳኔ ማድረግ ይኖርብናል። (ኤፌ. 6:11፤ 1 ጴጥ. 5:8, 9) አንዳንዶች ይሖዋን ለመተው ቢወስኑም እንኳ እኛ ለእሱ ያለንን ታማኝነት ጠብቀን እንኖራለን፤ እሱ ወሮታችንን እንደሚከፍለንም እንተማመናለን።—2 ሳሙ. 22:26

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2026)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2026 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ