ከሐምሌ 14-20
ምሳሌ 22
መዝሙር 79 እና ጸሎት | የመግቢያ ሐሳብ (1 ደቂቃ)
1. ልጆችን ለማሳደግ የሚረዱ ጠቃሚ መሠረታዊ ሥርዓቶች
(10 ደቂቃ)
ልጆቻችሁን ለሕይወት ውጣ ውረድ አዘጋጇቸው (ምሳሌ 22:3፤ w20.10 27 አን. 7)
ከተወለዱበት ጊዜ አንስቶ አሠልጥኗቸው (ምሳሌ 22:6፤ w19.12 26 አን. 17-19)
ፍቅራዊ ተግሣጽ ስጧቸው (ምሳሌ 22:15፤ w06 4/1 9 አን. 4)
2. መንፈሳዊ ዕንቁዎች
(10 ደቂቃ)
ምሳሌ 22:29—ይህን ጥቅስ ከጉባኤ እንቅስቃሴዎች ጋር በተያያዘ በሥራ ላይ ማዋል የምንችለው እንዴት ነው? ይህስ ምን ጥቅም ያስገኛል? (w21.08 22 አን. 11)
ከዚህ ሳምንት የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ምን መንፈሳዊ ዕንቁዎች አግኝታችኋል?
3. የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ
(4 ደቂቃ) ምሳሌ 22:1-19 (th ጥናት 10)
4. ውይይት መጀመር
(3 ደቂቃ) ከቤት ወደ ቤት። (lmd ምዕራፍ 5 ነጥብ 4)
5. ውይይት መጀመር
(4 ደቂቃ) መደበኛ ያልሆነ ምሥክርነት። ግለሰቡ ለወላጆች የሚጠቅም መረጃ ከjw.org ላይ ማግኘት የሚችለው እንዴት እንደሆነ አሳየው። (lmd ምዕራፍ 1 ነጥብ 4)
6. ንግግር
(5 ደቂቃ) ijwyp ርዕስ 100—ጭብጥ፦ የወላጆቼን ሕግ ጥሻለሁ—ምን ባደርግ ይሻላል? (th ጥናት 20)
መዝሙር 134
7. ታጋሽ ሁኑ፤ ሆኖም ልል አትሁኑ
(15 ደቂቃ) ውይይት።
ልጆችን ማሳደግ ከፍተኛ ትዕግሥት ይጠይቃል። ወላጆች ለልጆቻቸው ያልተከፋፈለ ትኩረትና ሰፊ ጊዜ ሊሰጧቸው ይገባል። (ዘዳ 6:6, 7) ወላጆች በልጆቻቸው ልብ ውስጥ ያለውን ነገር ለማወቅ ጥያቄዎችን በመጠቀም የልባቸውን ቀድተው ማውጣትና ሐሳባቸውን ሲገልጹ በጥሞና ማዳመጥ ይኖርባቸዋል። (ምሳሌ 20:5) በተጨማሪም ወላጆች ልጆቻቸው አንድን መመሪያ መረዳትና በሥራ ላይ ማዋል እንዲችሉ መመሪያውን በተደጋጋሚ መናገር ሊያስፈልጋቸው ይችላል።
ይሁንና ታጋሽ የሆኑ ወላጆች ልል አይደሉም። ይሖዋ ለልጆቻቸው ገደብ የማውጣት እንዲሁም ልጆቻቸው ሲያጠፉ የመገሠጽ ሥልጣን ሰጥቷቸዋል።—ምሳሌ 6:20፤ 23:13
ኤፌሶን 4:31ን አንብብ። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦
ወላጆች ተቆጥተው ሳለ ለልጆቻቸው ተግሣጽ መስጠት የሌለባቸው ለምንድን ነው?
ገላትያ 6:7ን አንብብ። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦
ወላጆች፣ ልጆቻቸው ለሠሩት ነገር መዘዙን እንደሚያጭዱ ማስተማራቸው አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
‘በትዕግሥት እርስ በርሳችሁ በፍቅር ተቻቻሉ’—ልጆቻችሁን የተባለውን አጭር ድራማ አጫውት። ከዚያም እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦
ከቪዲዮው ምን ትምህርት አግኝታችኋል?
8. የጉባኤ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
(30 ደቂቃ) lfb “የበላይ አካሉ መልእክት፣” የክፍል 1 ማስተዋወቂያ እና ትምህርት 1