የመስክ አገልግሎት ጎላ ያሉ ገጽታዎች
በ2015 ከተካሄደው የአቅኚነት አገልግሎት ትምህርት ቤት ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ስንገልጽላችሁ ደስ ይለናል። ነሐሴ 2015 በሰባት ከተሞች ውስጥ ማለትም በሶዶ፣ በሻሸመኔ፣ በአለታ ወንዶ፣ በአርባ ምንጭ፣ በአዲስ አበባ፣ በአዳማና በጅማ 15 ትምህርት ቤቶች ተካሂደው ነበር። ወደ 465 የሚጠጉ አቅኚዎች በትምህርት ቤቱ መካፈል ችለዋል። ከእነዚህ መካከል 176 የሚያህሉት በትምህርት ቤቱ ለሁለተኛ ጊዜ የመካፈል አጋጣሚ ያገኙ ተሞክሮ ያላቸው አቅኚዎች ናቸው።
የበላይ አካሉ ባደረገው ፍቅር የተንጸባረቀበት ዝግጅት የተነሳ የቤቴል ቤተሰብ አባላትም በዚህ ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ በትምህርት ቤቱ መካፈል ችለዋል። ሁሉም ለዚህ አዲስ ዝግጅት ምስጋናቸውን ገልጸዋል።
ይህ ትምህርት ቤት አቅኚዎች ‘አገልግሎታቸውን በተሟላ ሁኔታ’ እንዲፈጽሙ ይረዳቸዋል የሚል እምነት አለን።—2 ጢሞ. 4:5