የመስክ አገልግሎት ጎላ ያሉ ገጽታዎች
በሐምሌ ወር 10,020 አስፋፊዎች ሪፖርት በማድረጋቸው በኢትዮጵያ ያሉ አስፋፊዎች ቁጥር ለመጀመሪያ ጊዜ ከ10,000 አልፏል! የዘወትር አቅኚዎች ቁጥር 1,940 የደረሰ ሲሆን ከ300 በላይ ልዩ አቅኚዎች አሉ። በአጠቃላይ 214 ጉባኤዎችና 34 ቡድኖች አሉ፤ ከእነዚህ ውስጥ 71 ጉባኤዎች የሚገኙት በአዲስ አበባ ነው። ይህ የሚያበረታታ ዜና ቢሆንም መጨረሻው እየደረሰ ከመሆኑ አንጻር መሠራት ያለበት ሰፊ ክልል አለ። ተጨማሪ ወንድሞች፣ የመንግሥቱ ሰባኪዎች ይበልጥ ወደሚያስፈልጉባቸው ቦታዎች ሄደው ለማገልገል ራሳቸውን እንደሚያቀርቡ ተስፋ እናደርጋለን። እንዲህ ያለ ውሳኔ ያደርጉ ወንድሞችና እህቶች የተትረፈረፈ በረከት በማጨድ ላይ ናቸው።